በደቡብ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ክልላዊ መንግስት የክልል ም/ቤት ጽ/ቤት
የደቡብ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ህዝቦች ክልል ምክር ቤት
የክልሉ መስተዳድር ምክር ቤት ሥልጣንና ተግባር በተሻሻለው የደቡብ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ክልል ሕገመንግሥት አንቀጽ 66 የተመለከተው ይሆናል፡፡
ራዕይ /vission
"እንደ ኢትዮጵያ አቆጣጠር በ2022 ለዲሞክራሲያዊና መልካም አስተዳደር መስፈን
አርአያ የሆነ ምክር ቤት መሆን ››
ተልዕኮ /Mission
በህዝብ የነቃ ተሳትፎ ለክልሉ ማኅበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ዕድገት መፋጠን ፋይዳ ያላቸውን
ህጎች በማውጣት፣ የመንግስት አካላትን በማደራጀት፣ አፈጻጸማቸውን በመከታተልና በመቆጣጠር የህዝብ የሥልጣን ባለቤትነት እንዲረጋገጥ፣
የግልጸኝነትና ተጠያቂነት አሠራር እንዲሰፍንና ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት እንዲጎለብት ማድረግ ነው፡፡
ዕሴቶች
/values
• ፍትሃዊነት መርሃችን ነው፡፡
• ህዝብን በቅንነት ማገልገል መታወቂያችን ነው፡፡
• የአሰራር ግልጸኝነትና ተጠያቂነት መለያችን ነው፡፡
• ለህግ የበላይነት መቆም ሥራችን ነው፡፡
• ልዩነታችን ውበታችን፤ ውበታችን አንድነታችን ነው፡፡
• አሳታፊነትና ቅንጅታዊ አሠራር መርሃችን ነው፡፡
• ለህዝብ ጥያቄ ፈጣን ምላሽ መስጠት ባህላችን ነው፡፡