...

በደቡብ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ክልላዊ መንግስት የመንግስት ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ

nomoto

መልዕክቶች

የቢሮ ኃላፊ መልእክት

የቢሮ ሃላፊ መልዕክት

በሀገራችን ብሎም በክልላችን የተጀመረው የለውጥ ጉዞ ተስፋ ሰጪ ነው።

ባለፉት 27 አመታት በነበረው ጨቋኝ ስርአት የብዙሀኑ ሳይሆን የጥቂት ግለሰቦች እና ቡድኖች ብቻ  ተጠቃሚነት ጎልቶ ይታይ ነበር።

ታዲያ ይህ ፍትሀዊነት የጎደለው አስተሳሰብ እና ተግባር ለሀገራችን ብሎም ለክልላችን ህዝቦች የእድገት ጸር ሆኖ ቆይቷል።

የህዝቡ አዳጊ ፍላጎት እያየለ መጥቶ ብዙሀኑ ስርአቱን በመቃወም አሁን ለታየው የለውጥ እና የተስፋ ጊዜ ምክንያት ሆኗል።

የህዝብን ፍላጎት በጊዜ ተረድቶ ለለውጥ መነሳሳት ደግሞ የአመራሩ ሚና የአንበሳውን ድርሻ ይወስዳል።

በየደረጃው ያለው ባለሙያም ተገልጋዩን ማህበረሰብ በሙያው ማገዝ እና ከአመራሩ ጋር በቅንጅት መስራት ሲችል የበለጸገች ኢትዮጵያን  ለመፍጠር ትልቅ ድርሻ ይኖረዋል።

Read More...
ኃላፊነትና ተግባር

የመንግስት ኮምዩኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ

ቢሮው የሚከተሉት ሥልጣንና ተግባራት ይኖሩታል፣

1.  የክልሉን መንግስት እና የርዕሰ መስተዳድሩ ቃል አቀባይ ሆኖያገለግላል፤

2.  የክልሉን መንግስት ኢንፎርሜሽን በማእከል አደራጅቶ ለሚመለከታቸው አካላት እና ለሚዲያ እንደአስፈላጊነቱ ያሰራጫል

3.  የክልሉ ዞኖችና ልዩ ወረዳዎች ሴክተር መስሪያ ቤቶች የህዝብ ግንኙነት ስራዎች ያስተባብራል፣

4.  የክልሉ ማዕከል ሴክተር መስሪያ ቤቶችን የኮሚዩኒኬሽን እና የሚዲያ ግንኙነት ስራ ያስተባብራል፣

Read More...

ራዕይ

ራእይ፤ ተልእኮ እና እሴቶች

ተቋሙ ተልእኮ

ሁሉአቀፍና አዳዲስ የኮሚዩኒኬሽን መገናኛ ቴክኖሎጅዎችን በመጠቀም ለህብረተሰቡ የማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ልማቶችን እንዲሁም የኢንቨስትመንት መረጃዎችን የሚሰጥ በጥናትና ምርምር የታገዘ አካታች የኮሚዩኒኬሽን አገልግሎት ለመስጠት የሚያስችል ምቹ አካባቢ መፍጠር ነው፡፡

Read More...
በደቡብ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ክልላዊ መንግስት የመንግስት ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ
Organization Type መንግስታዊ
Services
Location ሀዋሳ
Status Active

የስራ ማስታወቂያዎች